ምርቶቻቸውን ለውጭ ገበያ የሚያቀርቡ ኩባንያዎችን ለመደገፍ ‹‹ብሔራዊ የኢንዱስትሪ ልማት ምክር ቤት››
በሚባል መጠሪያ የተቋቋመውን ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ይመሩታል::
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰሞኑን ባፀደቀው ደንብ መሠረት የተቋቋመው ይህ ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ
ምርቶችን ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ኩባንያዎችን የሚደግፉ መመርያዎችን ከማውጣት ባሻገር፣ ኩባንያዎች ያሉባቸውን
ችግሮች በመፍታት በኩል ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ተብሏል:: ቀደም ሲል ብሔራዊ የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ
የኢትዮጵያን ምርቶች ወደ ውጭ የሚልኩ ኩባንያዎችን ሲደግፍና ሲያበረታታ እንደነበር የሚታወስ ነው::
ይህንን የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ ወደ ምክር ቤት ደረጃ ማሳደግ ያስፈለገው፣ ኩባንያዎቹ የሚሰጣቸውን
ድጋፎች ለማብዛትና የምክር ቤቱን ተሳታፊዎች ከፍ ለማድረግ ታስቦ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ አብተው
ለሪፖርተር ገልጸዋል::
በዚህ መነሻነት ቀደም ሲል የነበረው ብሔራዊ የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ በመንግሥት ኤጀንሲዎች
ታጥሮ የነበረ በመሆኑ፣ በአዲሱ ምክር ቤት ውስጥ በወጪ ንግድ ተሳታፊ የሆኑ የግሉ ዘርፍ አባላትን እንደሚያቅፍ
ተነግሯል::
‹‹ምክር ቤቱ የሚመለከታቸው ጉዳዮች እንዲበዙ ከመደረጉም በተጨማሪ፣ የኤክስፖርት ዘርፍ አፈጻጸምን
በቅርበት ይከታተላል፤›› ሲሉ አቶ አህመድ አክለው ገልጸዋል:: ኢትዮጵያ በ2003 ዓ.ም. ባፀደቀችው የዕድገትና
ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የአገሪቱን ኢኮኖሚ በመምራት ላይ የሚገኘው የግብርና ዘርፍም ሆነ፣ የዕቅዱ ዘመን ማብቂያ
ከሆነው 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ኢኮኖሚውን የመምራቱን ተግባር ከግብርና ይረከባል ከተባለው ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ
ብዙ ይጠበቃል::
በ2006 ዓ.ም. የበጀት ዓመት መንግሥት በአጠቃላይ ከኤክስፖርት ዘርፍ 5.3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዷል::
ከዚህ ውስጥ 1.3 ቢሊዮን ዶላር ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ እንደሚገኝ ሲታቀድ፣ የተቀረውን ከማዕድን፣ ሆርቲካልቸርን
ጨምሮ ከግብርናው ዘርፎች እንደሚገኝ ታሳቢ ተደርጓል:: ምንጮች እንደገለጹት፣ በጠቅላይ ሚኒስትር
ኃይለ ማርያም ይመራ የነበረው የቀድሞ ብሔራዊ የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ ከአንድ ወር በፊት ከሁሉም ዘርፎች በ2006
ዓ.ም. ይገኛል በተባለው ገቢ ባለመርካቱ ዕቅዱ በድጋሚ ተለጥጦ እንዲቀርብለት አዟል::
ቀደም ሲል በአጠቃላይ የቀረበለት የኤክስፖርት ገቢ ምጣኔ ከ4.5 ቢሊዮን ብር የማይበልጥ ነበር:: ተለጥጦ ይቅረብ ተብሎ
ከተወሰነ በኋላ ሁሉም የኤክስፖርት ዘርፎች በድጋሚ ያሏቸውን አማራጮች እየገመገሙ የገቢ ዕቅዳቸውን ከፍ ማድረጋቸው ተመልክቷል::
በ2005 ዓ.ም. ከኤክስፖርት ይገኛል ተብሎ የታቀደው አምስት ቢሊዮን ዶላር የነበረ ቢሆንም፣ በተጨባጭ የተገኘው ግን 3.08 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው::
ከማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተገኘው ደግሞ ከተጠበቀው በታች 300 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት ከዚህ ቁጥር እጅግም ከፍ ያላለ ገቢ እንደሚገኝ ነበር የታቀደው:: አቶ አህመድ የቀረበው የኤክስፖርት ገቢ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ከማሳካት
አንፃር ያነሰ ነበር ብለው፣ በድጋሚ ከተከለሰ በኋላ በሚቀጥለው ዓመት የዕቅዱን 80 በመቶ ለማሳካትና በትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመኑ መጨረሻ በሚታቀደው ዕቅድ ላይ 20 በመቶ ተጨማሪ ተደርጎ ይታቀዳል ብለዋል:: በዚህም የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ እንደሚሳካ ያላቸውን እምነት ጨምረው ገልጸዋል:: አቶ አህመድ ምክንያታቸውን ሲያስረዱ በአሁኑ ጊዜ ኩባንያዎች ከአቅማቸው በታች የሚያመርቱና ምርታማነታቸውና ከመንግሥት የሚሰጣቸው ድጋፍም አነስተኛ መሆኑ በግምገማ የተደረሰባቸው ነጥቦች መሆናቸውን ገልጸው፣ በእነዚህ ነጥቦች ላይ ቀጣይ ሥራ እንደሚሠራ ታሳቢ በማድረግ የቀድሞ ዕቅድ ተከልሶ እንዲቀርቡ መደረጉን አስረድተዋል::
በሚባል መጠሪያ የተቋቋመውን ምክር ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ይመሩታል::
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰሞኑን ባፀደቀው ደንብ መሠረት የተቋቋመው ይህ ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ
ምርቶችን ለዓለም ገበያ ለማቅረብ ኩባንያዎችን የሚደግፉ መመርያዎችን ከማውጣት ባሻገር፣ ኩባንያዎች ያሉባቸውን
ችግሮች በመፍታት በኩል ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ተብሏል:: ቀደም ሲል ብሔራዊ የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ
የኢትዮጵያን ምርቶች ወደ ውጭ የሚልኩ ኩባንያዎችን ሲደግፍና ሲያበረታታ እንደነበር የሚታወስ ነው::
ይህንን የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ ወደ ምክር ቤት ደረጃ ማሳደግ ያስፈለገው፣ ኩባንያዎቹ የሚሰጣቸውን
ድጋፎች ለማብዛትና የምክር ቤቱን ተሳታፊዎች ከፍ ለማድረግ ታስቦ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ አብተው
ለሪፖርተር ገልጸዋል::
በዚህ መነሻነት ቀደም ሲል የነበረው ብሔራዊ የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ በመንግሥት ኤጀንሲዎች
ታጥሮ የነበረ በመሆኑ፣ በአዲሱ ምክር ቤት ውስጥ በወጪ ንግድ ተሳታፊ የሆኑ የግሉ ዘርፍ አባላትን እንደሚያቅፍ
ተነግሯል::
‹‹ምክር ቤቱ የሚመለከታቸው ጉዳዮች እንዲበዙ ከመደረጉም በተጨማሪ፣ የኤክስፖርት ዘርፍ አፈጻጸምን
በቅርበት ይከታተላል፤›› ሲሉ አቶ አህመድ አክለው ገልጸዋል:: ኢትዮጵያ በ2003 ዓ.ም. ባፀደቀችው የዕድገትና
ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የአገሪቱን ኢኮኖሚ በመምራት ላይ የሚገኘው የግብርና ዘርፍም ሆነ፣ የዕቅዱ ዘመን ማብቂያ
ከሆነው 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ኢኮኖሚውን የመምራቱን ተግባር ከግብርና ይረከባል ከተባለው ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ
ብዙ ይጠበቃል::
በ2006 ዓ.ም. የበጀት ዓመት መንግሥት በአጠቃላይ ከኤክስፖርት ዘርፍ 5.3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት አቅዷል::
ከዚህ ውስጥ 1.3 ቢሊዮን ዶላር ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ እንደሚገኝ ሲታቀድ፣ የተቀረውን ከማዕድን፣ ሆርቲካልቸርን
ጨምሮ ከግብርናው ዘርፎች እንደሚገኝ ታሳቢ ተደርጓል:: ምንጮች እንደገለጹት፣ በጠቅላይ ሚኒስትር
ኃይለ ማርያም ይመራ የነበረው የቀድሞ ብሔራዊ የኤክስፖርት ማስተባበሪያ ኮሚቴ ከአንድ ወር በፊት ከሁሉም ዘርፎች በ2006
ዓ.ም. ይገኛል በተባለው ገቢ ባለመርካቱ ዕቅዱ በድጋሚ ተለጥጦ እንዲቀርብለት አዟል::
ቀደም ሲል በአጠቃላይ የቀረበለት የኤክስፖርት ገቢ ምጣኔ ከ4.5 ቢሊዮን ብር የማይበልጥ ነበር:: ተለጥጦ ይቅረብ ተብሎ
ከተወሰነ በኋላ ሁሉም የኤክስፖርት ዘርፎች በድጋሚ ያሏቸውን አማራጮች እየገመገሙ የገቢ ዕቅዳቸውን ከፍ ማድረጋቸው ተመልክቷል::
በ2005 ዓ.ም. ከኤክስፖርት ይገኛል ተብሎ የታቀደው አምስት ቢሊዮን ዶላር የነበረ ቢሆንም፣ በተጨባጭ የተገኘው ግን 3.08 ቢሊዮን ዶላር ብቻ ነው::
ከማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተገኘው ደግሞ ከተጠበቀው በታች 300 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን፣ በሚቀጥለው ዓመት ከዚህ ቁጥር እጅግም ከፍ ያላለ ገቢ እንደሚገኝ ነበር የታቀደው:: አቶ አህመድ የቀረበው የኤክስፖርት ገቢ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱን ከማሳካት
አንፃር ያነሰ ነበር ብለው፣ በድጋሚ ከተከለሰ በኋላ በሚቀጥለው ዓመት የዕቅዱን 80 በመቶ ለማሳካትና በትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመኑ መጨረሻ በሚታቀደው ዕቅድ ላይ 20 በመቶ ተጨማሪ ተደርጎ ይታቀዳል ብለዋል:: በዚህም የትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ እንደሚሳካ ያላቸውን እምነት ጨምረው ገልጸዋል:: አቶ አህመድ ምክንያታቸውን ሲያስረዱ በአሁኑ ጊዜ ኩባንያዎች ከአቅማቸው በታች የሚያመርቱና ምርታማነታቸውና ከመንግሥት የሚሰጣቸው ድጋፍም አነስተኛ መሆኑ በግምገማ የተደረሰባቸው ነጥቦች መሆናቸውን ገልጸው፣ በእነዚህ ነጥቦች ላይ ቀጣይ ሥራ እንደሚሠራ ታሳቢ በማድረግ የቀድሞ ዕቅድ ተከልሶ እንዲቀርቡ መደረጉን አስረድተዋል::